” የኢትዮጽያ የፌዴራል ጠበቆች ማህበር”

ትላንት በአዋጅ ቁጥር1249/2013 አንቀፅ 57(1) መሠረት የተቋቋመው “የኢትዮጽያ የፌዴራል ጠበቆች ማህበር” ጠቅላላ ጉባኤ ፕሬዝዳንቱን እና ምክትል ፕሬዜዳንቱን መርጧል።

በዚህም ወ/ሮ ስንዱ አለሙ ኘሬዘዳንት ፤ አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸው ደግሞ ምክትል ኘሬዘዳንት ሆነው ተመርጠዋል።

የፍትህ ሚኒስቴር በህጉ በተደነገገው መሰረት ጉባዔውን በመጥራት የማህበሩ ፕሬዘዳንት እና ም/ል ፕሬዘዳፈንት እንዲሁም የስራ አስፈጻሚ ቦርድ አባላት እንዲመረጡ አድርጓል።

በተመሳሳይ ጠቅላላ ጉባኤው 7 /ሰባት/ የስራ አስፈፃሚ አባላትን መርጧል።
በዚህም መሠረት:-

  1. ሂሩት መለሠ; 634
  2. ፊሊጶስ አይናለም; 628,
  3. ሊቁ ወርቁ; 522,
  4. ዮሴፍ አዕምሮ;514,
  5. ሆሳና ነጋሽ; 492,
  6. ትደነቂያለሽ ተስፋ;424,
  7. ሰለሞን እምሩ; 418,

የስራ አስፈጻሚ አባል ሆነው ትላንት ተመርጠዋል።

About the Author

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

You may also like these